Pages

Saturday, October 27, 2018

ማኅሌተ ጽጌ:ሥርዓተ ማኅሌት ዘዘመነ ጽጌ "፬ኛ ሳምንት"

ማኅሌት ዘያሬድ:
ሥርዓተ ማኅሌት ዘዘመነ ጽጌ "፬ኛ ሳምንት" "በዓለ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቀ ጳጳሳት፣ ወሮማኖስ ሰማዕት" "ጥቅምት ፲፰"

ቅዱስ እስጢፋኖስ --- St.Estifani

                                           
🌹💚የቅዱስ እስጢፋኖስ ታሪክ ባጭሩ🌹💚

🌿❤️ እስጢፋኖስ የግሪክ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም «አክሊል» ማለት ነው።

🌿❤️ ቅዱስ እስጢፋኖስ በግሪክ ሀገር እንደተወለደ የሚነገርለትና ከክርስቶስ እርገት በኋላም አስራ ሁለቱም ሐዋርያት በጋራ ተሰብስበውና ለአገለግሎት ከመረጡዋቸው ሰባት ዲያቆናት አንዱና ዋነኛው ነበር። ሕዝቡን በማዕድ ያገለግሉ ዘንድ ሰባት ዲያቆናት ተመርጠዋል።
🌿❤️ ከእነዚህ መካከል ቅዱስ እስጢፋኖስ አንዱ ሲሆን ለስድስቱ ዲያቆናት ደግሞ አለቃ ሊቀ ዲያቆን ሆኖ ተሹሟል። ቅዱስ እስጢፋኖስ በማዕድ አገልግሎት ሕዝቡን ከማገልገሉ በተጨማሪ ወንጌልን ይሰብክ ነበር ። ተዐምራትን የማድረግ ጸጋም ተሰጥቶት ነበር በዚህም አገልግሎቱ ብዙዎችን ወደ ክርስትና መልሷል።
🌿❤️ በዚህም አይሁድ በቅናት ተነሳስተው

Tuesday, October 23, 2018

Wednesday, September 19, 2018

፹፩ (81) መፅሐፍ ቅዱስ እና ፷፮ (66)

♦በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ! ♦

★መናፍቃኑ ከስልሣ ስድስቱ ውጭ ሌሎች ቅዱሳት መጽሐፍት የለም ወይም አያስፈልግም እንዳይሉ ማስረጃዎችን እነሆ፡-

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን 


#አንድ_ጌታ
#አንድ_ሀይማኖት
#አንድ_ጥምቀት ። (ኤፌ 4፥5)
መጽሐፍትን ማስተዋልና መመርመር ያስፈልጋል ።
✍ ጥንት አባቶቻችን በዘመናቸው መናፍቃን ካህናት፣አላውያን መኳንት ፣ ከሀዲያን ነገስታት ሲነሱባቸው ብራና ደምጠው ፣ ቀለም በጥብጠው ፣ ብዕር ቀርፀው ፣ ተግሳስ ጽፈው በቂ ምላሾችን ሲሰጡ ቆይተዋል። አርዮስ ሲነሳ ፤ አትናቲዮስ ፣ ንስጥሮስ ሲነሳ ፤ ቄርሎስ በቂና ከበቂ በላይ የሆኑ መልሷቻቸውን መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርገው ሰተዋል። ዛሬላይ በዘመናችን እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች እንዲሁም ዕለት ዕለት እየተስፋፋ የመጣውን የምንፍቅናን ትምህርት ጥንት አባቶቻችን በዘመናቸው ሲያደርጉት እንደነበረው